የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2032 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ወደ 242 ለማድረስ ማቀዱን አስታወቀ

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2032 ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ወደ 242 ለማድረስ ማቀዱን አስታወቀ

ይህ የተገለጸው የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት እና የኢትዮጵያ የጥራት ሽልማት ድርጅት የበላይ ጠባቂ ታዬ አፅቀሥላሴ የአየር መንገዱን የሥራ እንቅስቃሴ ተዘዋውረው በጎብኙበት ወቅት ነው፡፡

አየር መንገዱን የሀገር ምልክት በማለት የገለጹት ርዕሰ ብሔሩ፤ “ተቋሙ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን ለማላቅ እያከናወናቸው ያሉ ሥራዎችን አጠናክሮ መቀጠል አለበት" ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፤ አየር መንገዱ ዓለም አቀፋዊና የሀገር ውስጥ መዳረሻዎቹን በማስፋት በ2032 ዓ.ም ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን ወደ 242 ለማድረስ አቅዷል ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0