ጥቁር አውራሪስ ከኢትዮጵያ መጥፋቱ ተገለፀ
19:45 13.03.2026 (የተሻሻለ: 19:54 13.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጥቁር አውራሪስ ከኢትዮጵያ መጥፋቱ ተገለፀ
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ከኢትዮጵያ ጥቁር አውራሪስን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ የጠፉ ዝርያዎች መኖራቸውን አስታወቋል።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኩመራ ዋቅጅራ፤ እስከ አሁን በጥናት ተደግፎ በቁጥር ባይረጋገጥም በርካታ የነፍሳት ዝርያዎች ከኢትዮጵያ ምድር መጥፋታቸውን እና ሌሎችም ለመጥፋት አደጋ መጋለጣቸውን አመልክተዋል።
አሁን ላይ በዘርፉ የማኅበረሰብ ግንዛቤ እና የመንግሥት ትኩረት መሻሻል እየታየ በመምጣቱ በቀጣይ ችግሮችን ለመፍታት ያስችላል ሲሉ መናገራቸውንም የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X