በሆርሙዝ ሰርጥ የሚፈጠር አለመረጋጋት መላ አፍሪካን ሊያናውጥ ይችላል - ኢትዮጵያዊ ምሁር
18:56 13.03.2026 (የተሻሻለ: 19:04 13.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሆርሙዝ ሰርጥ የሚፈጠር አለመረጋጋት መላ አፍሪካን ሊያናውጥ ይችላል - ኢትዮጵያዊ ምሁር
አፍሪካ በገቢ ነዳጅ እና በዓለም አቀፍ የባሕር ትራንስፖርት መስመሮች ላይ ጥገኛ መሆኗ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚከሰቱ አለመረጋጋቶች ተጋላጭ ያደርጋታል ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የማኅበራዊና ኢኮኖሚ ተመራማሪ መሀመድ ኢብራሂም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
"ይህ ተጋላጭነት አፍሪካ የራሷን የነዳጅ ማጣሪያ አቅም በማስፋፋት የኢነርጂ ደህንነቷን ማጠናከር እንዳለባት ያሳያል" ብለዋል።
ኢብራሂም አፍሪካ ከኢኮኖሚ መስተጓጉሎች ራሷን ለመጠበቅ ሁለት ዋና ዋና መፍትሄዎችን ጠቁመዋል፦
የአፍሪካ አኅጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣናን መጠቀም፦ ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ውጭ መላክ እና ውድ የተጣሩ የነዳጅ ውጤቶችን ከውጭ ማስገባት ማቆም።
ቀጣናዊ የኢነርጂ ትብብርን ማጠናከር፦ የነዳጅ ማጣሪያዎችን በጋራ መጠቀም እና ድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታዎችን መገንባት።
"ይህም የአምራች እና የኢንዱስትሪ ዘርፉ እሴት የተጨመረባቸውን ምርቶች በሀገር ውስጥ እንዲያመርት ለማበረታታት አስፈላጊ ነው" ሲሉ ንግግራቸውን አጠቃለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X