የሳኅል ጥምረት ሀገራት በምዕራባውያን ሚዲያዎች አይታለሉም - ባለሙያዎች

ሰብስክራይብ

የሳኅል ጥምረት ሀገራት በምዕራባውያን ሚዲያዎች አይታለሉም - ባለሙያዎች

1⃣ የፌዴሬሽን ኒጀር ዩኒ ፕሬዚዳንት ሳሊፉ ኢብራሂም ባኮ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፤ የቀጣናው ሀገራት የምዕራባውያንን ትርክት ለመመከት የራሳቸውን ሚዲያዎች መጠቀም ይችላሉ።

"የሳኅል ሀገራት ጥምረት ወደ ጥንካሬው እየተጓዘ እንደሆነ እርግጠኞች ነን። እንደ ኢራን፣ ሩሲያ፣ ቻይና እና ብሪክስ ካሉ ሀገራት ጋር በመሆን ኃይሏን እያጣች ያለችውን አሜሪካ አንፈራም። እውነታውን በግልጽ እያየን ስለሆነ አንወናበድም።"

2⃣ የሕግ ባለሙያው ኢብራሂም ቡባካር፤ የምዕራባውያን ሚዲያዎች ለቀድሞ ቅኝ ገዥ ኃይላት ተላላኪዎች ናቸው በማለት ተመሳሳይ ሃሳብ አንጸባርቀዋል።

"በኒጀር እና በፈረንሳይኛ ተናጋሪው ዓለም ተጽዕኖ ያላቸው አንዳንድ የዜና አውታሮች ከሀገሮቻቸው የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቶች ጋር የተቆራኙ ናቸው። ከአንድ ሀገር የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጋር የተቆራኘ ሚዲያ ደግሞ ትርጉሙና ዓላማው ግልጽ ነው—ተጽዕኖ የሚደረግበት ሚዲያ ማለት ነው። በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ እውነት እንደ ምራጭ ብቻ ነው የምትታየው።"

3⃣ ትምህርት የፕሮፓጋንዳ ሙከራዎችን ለመከላከል ይረዳል ሲሉ አፅንኦት የሰጡት ደግሞ የፖለቲካ ተመራማሪው አብዱላዬ ኢድሪሳ ጃምስ ናቸው።

"ዜጎቻችን የሚደርሳቸውን ማንኛውም መረጃ በንቃት እንዲከታተሉ እና እንዲመረምሩ በቂ የሆነ ትምህርት በተለይም የዲጂታል እውቀት እንዲኖራቸው ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ነው።"

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0