የኢትዮጵያ በ31 በመቶ እድገት በአየር መንገድ የማሳፈር አቅም ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ በ31 በመቶ እድገት በአየር መንገድ የማሳፈር አቅም ከአፍሪካ ቀዳሚ ሆነች

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እ.ኤ.አ. በ2026 የመቀመጫ (የማሳፈር/ወንበር) መጠኑ 17 ሚሊዮን ገደማ ደርሷል። ይህ ከፍተኛ ጭማሪ ኢትዮጵያን በአኅጉሪቱ ካሉ ተንቀሳቃሽ የአቪዬሽን ማዕከላት አንዷ እንድትሆን አድርጓታል፡፡ ለአጠቃላይ የአፍሪካ አቪዬሽን ዕድገትም ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተች ትገኛለች።

አየር መንገዱ በመጋቢት (ማርች) 2026 ብቻ ወደ ሁለት ሚሊዮን በሚሆን መቀመጫ መሪነት ቀጥሎበታል። ይህ የአቅም ጭማሪ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ75,300 መቀመጫዎች ብልጫ ያለው አለው፡፡ ይህም አየር መንገዱ በዘርፉ ያለውን የበላይነት ያሳያል።

በአዲስ አበባ የሚገኘው የአየር መንገዱ ማዕከል በአኅጉሪቱ የሚደረጉ ዓለም አቀፍ ጉዞዎችን በማቀላጠፍ ረገድ ማዕከላዊ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ ኢትዮጵያን ለቱሪዝምም ሆነ ለንግድ ጉዞዎች ወሳኝ መግቢያ እንዳደረጋትም መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0