የመጀመሪያ ደረጃ የምርመራ ውጤቶች በኢራን የሴቶች ትምህርት ቤት ለተፈጸመው ጥቃት አሜሪካ ተጠያቂ መሆኗን ያሳያሉ ተባለ
20:09 11.03.2026 (የተሻሻለ: 20:14 11.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የመጀመሪያ ደረጃ የምርመራ ውጤቶች በኢራን የሴቶች ትምህርት ቤት ለተፈጸመው ጥቃት አሜሪካ ተጠያቂ መሆኗን ያሳያሉ ተባለ
የካቲት 20 ቀን በኢራን ሚናብ ከተማ የሴቶች የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ በቶማሃውክ ሚሳኤሎች የተፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት በአሜሪካ መፈጸሙን የወታደራዊ ምርመራ ማረጋገጡን ኒው ዮርክ ታይምስ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው የአሜሪካ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
እንደ ዘገባው ከሆነ፣ በአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ውስጥ የሚገኙ መኮንኖች ጥቃቱ የተፈጸመበትን ቦታ ነጥቦች ያዘጋጁት፣ በመከላከያ ደህንነት ኤጀንሲ በተሰጠ ጊዜው ያለፈበት መረጃ በመነሳት ነው።
ባለሥልጣናቱ እንደገለጹት፣ የምርመራው ውጤት አሁንም የመጀመሪያ ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን፣ አሁን ያለው ዋናው ጥያቄ ለምን ጊዜው ያለፈበት መረጃ ሳይጣራ ለምን ጥቅም ላይ እንደዋለ ማወቅ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X