የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ባለፉት ሁለት ወራት 1,434 የታጠሩ የሰፈር ውስጥ መንገዶችን ማስከፈቱን አስታወቀ
18:39 11.03.2026 (የተሻሻለ: 18:44 11.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን ባለፉት ሁለት ወራት 1,434 የታጠሩ የሰፈር ውስጥ መንገዶችን ማስከፈቱን አስታወቀ
የባለሥልጣኑ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢያሱ ሰሎሞን እንደገለጹት፣ በሁሉም ክፍለ ከተሞች በተካሄደ ጥናት 2,438 የሰፈር መንገዶች በአጥሮች ወይም በሌሎች እንቅፋቶች ተዘግተው መገኘታቸው ተረጋግጧል፡፡
ይህም በመኖሪያ አካባቢዎች ያለውን እንቅስቃሴ በመገደብ በከተማዋ የትራንስፖርት ትስስር ላይ ጫና ፈጥሯል።
እንደ ባለሥልጣኑ መረጃ ከሆነ፤ አሁንም ከ1,000 በላይ የሚሆኑ ተዘግተው የሚገኙ መንገዶች በግምገማ ላይ ይገኛሉ፡፡ በሚቀጥሉት ወራት ውስጥ ሊከፈቱ እንደሚችሉ ተመላክቷል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X