በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ 21ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ በዌስተርን ኢኳቶሪያ ኒዛራ ሆስፒታል የመድኃኒትና ድጋፍ አደረገ
17:00 11.03.2026 (የተሻሻለ: 17:04 11.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በደቡብ ሱዳን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ 21ኛ ሞተራይዝድ ሻለቃ በዌስተርን ኢኳቶሪያ ኒዛራ ሆስፒታል የመድኃኒትና ድጋፍ አደረገ
በፓዙ ካምፕ የክሊኒክ ኃላፊ ሻለቃ ዶክተር ፍቃዱ ሁምኔሳ፣ ሠራዊቱ የቀጣናው ሰላም ይበልጥ እንዲሻሻል የሠላም ማስከበር ተልዕኮውን በስኬት ከመፈፀም ባሻገር ለኒዛራ ሆስፒታል ያደረገው የመድኃኒትና የምግብ ድጋፍ ህዝባዊ ባሕሪውን ያሳየና ሰብዓዊነትን ያረጋገጠ በጎ ተግባር እንደሆነ አብራርተዋል።
ሠራዊቱ በዚሁ ድጋፉ ሳያበቃ በማኅበረሰብ አቀፍ ስራዎች የሚያደርገው ተሳትፎ በተልዕኮው ተመራጭ እንዲሆን አስችሎታል ሲል መከላከያ በማኅበራዊ የትስስር ገፁ ፅፏል።
የኒዛራ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ታባን ቻርለስ ሠላም አስከባሪዎቹ ከሕብረተሰቡ ጋር ያላቸው መልካም ግንኝነት የሚደነቅ እንደሆነ ተናግረው ለሆስፒታሉ ያደረጉት ድጋፍ በማኅበረሰቡ ስም ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

