የሳህል ሀገራት ጥምረት ራስን መቻል ህልም ብቻ ሳይሆን ሊተገበር እንደሚቻል አሳይቷል - ኢትዮጵያዊት የፓን-አፍሪካኒዝም አራማጅ

ሰብስክራይብ

የሳህል ሀገራት ጥምረት ራስን መቻል ህልም ብቻ ሳይሆን ሊተገበር እንደሚቻል አሳይቷል - ኢትዮጵያዊት የፓን-አፍሪካኒዝም አራማጅ

​የሳህል ሀገራት ጥምረት የራሱ የሆነ የኢንቨስትመንት ባንክ፣ የጋራ ወታደራዊ ጥረቶች እና የህዝብ አመለካከት ትርክት ላይ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችል የሚዲያ መድረክ በመፍጠር ትልቅ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን የፓን-አፍሪካኒዝም ይዘት ፈጣሪ ወንጌል ዘላለም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

​"ለስላሳ ኃይል ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ጉዳይ ነው" ያሉት ወንጌል፣ ከታሪካዊ ተፅዕኖዎች ለመላቀቅ የራስን ትርክት መቆጣጠር ያለውን ፋይዳ አስገንዝበዋል።

​እንደ ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ያሉ ሀገራት የራሳቸውን ታሪክ በአካባቢያቸው ቋንቋዎች በመንገር፣ የአስተሳሰብ ቅኝ አገዛዝን ማስወገድ፣ የራሳቸውን የወደፊት ዕጣ ፈንታ መወሰን እና በውጫዊ ጫናዎች ላይ መተባበር እንደሚችሉ ገልፀዋል።

ፓን-አፍሪካኒዝም በዓለም ዙሪያ ያሉ ጥቁር ህዝቦችን እንዴት እያስተባበረ እንደሚገኝ እና የጋራ አቅም እውን ሊሆን እንደሚችል ለመረዳት ቪዲዮውን ይመልከቱ።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0