"የኢራንን መንግሥት መለወጥ ወይም አለመለወጥ የራሱ የኢራን ህዝብ ውሳኔ ነው"- የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia"የኢራንን መንግሥት መለወጥ ወይም አለመለወጥ የራሱ የኢራን ህዝብ ውሳኔ ነው"- የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ
የኢራንን መንግሥት መለወጥ ወይም አለመለወጥ የራሱ የኢራን ህዝብ ውሳኔ ነው- የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.03.2026
ሰብስክራይብ

"የኢራንን መንግሥት መለወጥ ወይም አለመለወጥ የራሱ የኢራን ህዝብ ውሳኔ ነው"- የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ

ይህ (መንግሥታትን መቀየር) የአሜሪካ ባህሪ አዲስ ባለመሆኑ ማንንም ሊያስገርም አይገባም፤  በአፍጋኒስታን፣ በኢራቅ እና በሊቢያ የታየ ሲሆን፣ በቅርቡ የተፈጸመው እና አሁንም እየቀጠለ ያለው ጥቃት የእርምጃዋ አንድ አካል ነው ሲሉ ዶክተር አብዱ መሐመድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"... አሜሪካ በኢራን ውስጥ በኃይል የገዥውን አካል ለመለወጥ የምታደርገው ሙከራ በግልጽ የሚያሳየው [...] እርምጃው ያለ ተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ይሁንታ መሆኑን ነው" ሲሉም የጥቃቶቹን ሕገ-ወጥነት ጠቅሰዋል።

አሜሪካ ባህረ ሰላጤው የሚገኙ ሀገራትን መጠበቅ አለመቸሏ ለሀገራቱ ጥሩ ተሞክሮ እንደሆነም ዶክተር አብዱ ያስረዳሉ።

"ወደ አካባቢያዊ የመከላከያ ልምምድ ወይም ወደ ሌሎች ኃይሎች፣ በተለይም ወደ ቻይና እና ሩሲያ ፊታቸውን የሚያዞሩበት ጊዜ ነው" በማለት ሀገራቱ የተሻለ ከለላ እንደሚያስፈልጋቸው አሳስበዋል።

ባለሙያው፣ አሁን ያለው የዓለም አቀፍ የፖለቲካ እድገት በግልጽ እንደሚያሳየው ምዕራባውያን ወይም አሜሪካ ከእንግዲህ የፕላኔቷ መሪዎች አለመሆናቸውን ያሳያል በማለት፣ የጂኦፖለቲካ ማዕከሉ ወደ ደቡባዊ ዓለም እያጋደለ መሆኑን አብራርተዋል።

​ "የደቡባዊ ዓለም ሀገራት አንድ ላይ መምጣት አለባቸው። እኔ እንደማስበው ለማንም የማይወግን ክልላዊ ጥምረት የመፍጠሪያው ጊዜ አሁን ነው።" ብለዋል፡፡

​በስተመጨረሻም፣ እየተካሄደ ያለው ጥቃት ለአሜሪካ እና ለእስራኤል ጉዳት ይሆናል፣ ምክንያቱም ኢራን እንደ ኢራቅ ሆነ እንደ ሊቢያ አይደለችም። እጅግ ሰፊ፣ እጅግ ብዙ ሕዝብ እና በጣም ስትራቴጂካዊ ሀገር ናት ሲሉ ዶክተር አብዱ መሐመድ ሀሳባቸውን ደምድመዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0