ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ለቱሉ ካፒ የወርቅ ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ 310 ሚሊዮን ዶላር የሚያስገኝለትን ስምምነት ፈጸመ
17:33 10.03.2026 (የተሻሻለ: 17:34 10.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ለቱሉ ካፒ የወርቅ ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ 310 ሚሊዮን ዶላር የሚያስገኝለትን ስምምነት ፈጸመ
ኩባንያው፣ ለቱሉ ካፒ ፕሮጀክት ግንባታ፣ የምህንድስና እና የአቅርቦት ስራዎችን የሚያከናውን የውል ስምምነት ከሊኮፖዲየም ኩባንያ ጋር መፈራረሙን አስታውቋል፡፡
ስምምነቱ የፕሮጀክቱ ግንባታ እና ተያያዥ የፋይናንስ ዝግጅቶች በተያዘላቸው እቅድ መሰረት እየተጓዙ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው ብሏል።
የመጀመሪያው የወርቅ ምርት እ.ኤ.አ. በ2028 መጀመሪያ ላይ እንደሚጀምር ኩባንያው መግለጹን የአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ዘግቧል።
ይህ ፕሮጀክት ከዕቅድ ወደ ትግበራ መሸጋገሩ በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ላይ ያለውን የኢንቨስትመንት ስጋት እንደሚቀንሰውና ለሀገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እንደሚያስገኝ ይጠበቃል ሲሉ የግል መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ ቪድዮ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X