ኢራን አስፈላጊ ሆኖ እስከተገኘ ድረስ የሚሳኤል ጥቃቷን ለመቀጠል ተዘጋጅታለች - የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
11:08 10.03.2026 (የተሻሻለ: 13:54 10.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢራን አስፈላጊ ሆኖ እስከተገኘ ድረስ የሚሳኤል ጥቃቷን ለመቀጠል ተዘጋጅታለች - የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
አባስ አራግቺ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ፦
ኢራን በጣም ከፍተኛ ልምድ ስላላት፣ ከአሜሪካውያን ጋር የመደራደር ጉዳይ ዳግም የመነሳቱ እድል ዝቅተኛ ነው፡፡
በሚናብ ለተገደሉት 168 ንጹሃን ሴት ተማሪዎች ሕይወት አሜሪካ ተጠያቂ ናት፡፡
አሜሪካ መንግሥትን በሁለት ወይም በሦስት ቀናት ውስጥ ገልብጣ ፈጣን ድል መቀዳጀት የምትችል መስሏት ነበር። ነገር ግን አልተሳካላትም፡፡
አሁን ባለው ሁኔታ፣ የአሜሪካ ድርጊቶች በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ግልጽና ቀውስ ፈጣሪ ተፅዕኖ እያሳደሩ መሆናቸውን ስንመለከት፣ ድርጊታቸው ምንም ዓይነት አመክንዮአዊ ዓላማ ያለው ሆኖ አናገኘውም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X