ፑቲን እና ትራምፕ በኢራን እና ዩክሬን ጉዳይ የስልክ ውይይት አደረጉ
09:50 10.03.2026 (የተሻሻለ: 09:54 10.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ትራምፕ በኢራን እና ዩክሬን ጉዳይ የስልክ ውይይት አደረጉ
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር በስልክ መወያየታቸውን የክሬምሊን ረዳት ዩሪ ኡሻኮቭ ተናግረዋል፡፡
እንደ ኡሻኮቭ ገለጻ፣ የስልክ ጥሪው በትራምፕ አቅራቢነት የተደረገ ሲሆን፣ ሁለቱ መሪዎች ትኩረታቸውን በኢራን ግጭት እና በዩክሬን ያለውን ሁኔታ በድርድር ለመፍታት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ አድርገዋል፡፡
ፑቲን በኢራን ያለውን ግጭት በፍጥነት በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችሉ ሐሳቦችን አቅርበዋል፡፡ ትራምፕ በግላቸው ያደረጉትን ጨምሮ አሜሪካ በዩክሬን ጉዳይ በሸምጋይነት የምታደርጋቸውን ጥረቶች በአዎንታዊ መልኩ ገምግመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X