አሜሪካ በኢራን ሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ከፈፀመችው ጥቃት ኃላፊነት ለመሸሽ ግልጽ ውሸት እየተጠቀመች ነው - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአሜሪካ በኢራን ሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ከፈፀመችው ጥቃት ኃላፊነት ለመሸሽ ግልጽ ውሸት እየተጠቀመች ነው - ባለሙያ
አሜሪካ በኢራን ሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ከፈፀመችው ጥቃት ኃላፊነት ለመሸሽ ግልጽ ውሸት እየተጠቀመች ነው - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.03.2026
ሰብስክራይብ

አሜሪካ በኢራን ሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ከፈፀመችው ጥቃት ኃላፊነት ለመሸሽ ግልጽ ውሸት እየተጠቀመች ነው - ባለሙያ

​በቴህራን በሴቶች ትምህርት ቤት ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ኢራንን ተጠያቂ ለማድረግ ከአሜሪካ የሚሰጡት መግለጫዎች፣ የአሜሪካ የጦር ስትራቴጂ መክሸፉን እና የኢራንን ያልተጠበቀ ጥንካሬ ሲያዩ የተፈጠረ የፖለቲካ ግራ መጋባት ምልክት ነው ሲሉ የዓለም አቀፍ የህዝብ ህግ ፕሮፌሰር ዶክተር መሐመድ መህራን ለስፑትኒክ ተናገሩ።

​ ባለሙያው እንዳሉት፣ የጥቃቱ ምንጭ የሆኑ ሪፖርቶች፣ የሳተላይት ምስሎች እና የምስክርነት ቃላት እንደሚያሳዩት ጥቃቱ የተፈጸመው በአሜሪካ "ቶማሃውክ" ሚሳይሎች ወይም በእስራኤል ሌዘር መሪ ቦምቦች መሆኑን ያረጋግጣሉ። በእንዲህ ዓይነት ትክክለኛ የጦር መሳሪያዎች የታገዘ ጥቃት "ድንገተኛ" ሊሆን እንደማይችልም አክለው አስረድተዋል።

​አሜሪካ ኢራንን ተጠያቂ ለማድረግ የምትጠቀምባቸው ወቅታዊ መግለጫዎች የሥነ-ልቦና ጦርነት አካል ናቸው ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ አያይዘውም፣ አሜሪካ ከዚህ ቀደም በኢራቅ፣ በአፍጋኒስታን እና በሊቢያ የሲቪል ህዝብ ሞትን በ"መረጃ ስህተት" ምክንያት እንደሆነ በማስመሰል ተመሳሳይ ዘዴዎችን ትጠቀም እንደነበር አስታውሰዋል።

​አሜሪካ የኢራንን የፖለቲካ ስርዓት የመደርመስ ዋና ወታደራዊ ግቧን ማሳካት ባለመቻሏ ከፍተኛ የሆነ የውስጥ ትችት እየገጠማት በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት በአጣብቂኝ ውስጥ ትገኛለች ያሉት ተንታኙ፣ ይህ ሁኔታም አሜሪካን ወደ ይበልጥ አደገኛ እርምጃዎች ሊገፋፋት እንደሚችል በማስጠነቀቅ ሃሳባቸውን ደምድመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0