በኢትዮጵያ 30 ሚሊዮን ሴቶችን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ተጀመረ
17:34 09.03.2026 (የተሻሻለ: 17:44 09.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ 30 ሚሊዮን ሴቶችን የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት ለማድረግ ያለመ ንቅናቄ ተጀመረ
የሴቶች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ ንቅናቄ ዓላማም በመጪው ሰኔ ወር እንደሀገር አጠቃላይ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር 90 ሚሊዮን ለማድረስ የተያዘውን ግብ ለማሳካት መሆኑን ተገልጿል።
🪪 የሴቶች ፋይዳ መታወቂያ ምዝገባና ብሔራዊ የምዝገባ መርሃግብር የማይነጣጠሉ እንደሆነ የገለጹት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና አስተባባሪ ዮዳሔ አርአያሥላሴ፣ እስካሁን ድረስ የፋይዳ መታወቂያ ተመዝጋቢ ዜጎች ቁጥር 37 ሚሊዮን መድረሱን አክለዋል።
ከአጠቃላይ ተመዝጋቢዎች ቁጥር 60 በመቶ ወንዶችና ቀሪዎቹ ሴቶች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X