የኢራን ጦርነት አሜሪካን ለአሉሚኒየም እጥረት ሊያጋልጣት ይችላል - ባለሙያ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢራን ጦርነት አሜሪካን ለአሉሚኒየም እጥረት ሊያጋልጣት ይችላል - ባለሙያ
የኢራን ጦርነት አሜሪካን ለአሉሚኒየም እጥረት ሊያጋልጣት ይችላል - ባለሙያ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.03.2026
ሰብስክራይብ

የኢራን ጦርነት አሜሪካን ለአሉሚኒየም እጥረት ሊያጋልጣት ይችላል - ባለሙያ

የኢንዱስትሪ ባለሙያው ሊዮኒድ ካዛኖቭ "ለረጅም ጊዜ ሊቀጥል የሚችለው የፋርስ ባሕረ ሰላጤ ግጭት ከቀጣናው አሉሚኒየም ለሚያስገቡ የአሜሪካ ሸማቾች የአቅርቦት መቋረጥ የሚፈጥር ነው። ይህ በዓመት እስከ 1 ሚሊዮን ቶን የሚደርሰውን የአሉሚኒየም ገቢ ምርት ለመተካት ሌሎች አማራጮችን መፈለግ አለባቸው ማለት ነው" ሲሉ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

ካናዳ ወይም ቻይና ለአሉሚኒየም አቅርቦት ያሉት ጥቂት አማራጭ ምንጮች እንደሆኑ ባለሙያው ጠቅሰዋል። ሆኖም የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የውጭ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ከሁለቱም ሀገራት መንግሥታት ጋር ያለውን ግንኙነት አስቀድሞ ስላሻከረው ብረቱን በተመጣጣኝ ዋጋ ለመግዛት አዳጋች እንደሚያደርገው አስረድተዋል።

"ስለዚህ አሉሚኒየም ወደ ሀገር ውስጥ በሚያስገቡ የአሜሪካ ኢንተርፕራይዞች ላይ የምርት መቀነስ እና በምርት ጭነቶች ዙሪያ የውል መቋረጦች ሊኖሩ ይችላሉ" ሲሉ ደምድመዋል።

በመጋቢት ወር መጀመሪያ ከዓለም ግዙፍ የአሉሚኒየም አምራቾች አንዱ የሆነው አሉሚኒየም ባህሬን፤ በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት መባባስ ምክንያት የአቅርቦት መቋረጥ ሊኖር እንደሚችል ለደንበኞቹ አስታውቆ ነበር።

ዓለም አቀፉ የአሉሚኒየም ኢንስቲትዩት እንደገለጸው፤ ባለፈው ዓመት የፋርስ ባሕረ ሰላጤ ሀገራት 6.16 ሚሊዮን ቶን የመጀመሪያ ደረጃ አሉሚኒየም ያመረቱ ሲሆን ይህም ከዓለም አቀፉ 73.78 ሚሊዮን ቶን ጠቅላላ ምርት ውስጥ 8.35 በመቶ የሚገመት ድርሻ ይይዛል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0