የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሀገራዊ የኃይል ምርት ድርሻ 51 በመቶ ደረሰ
15:38 08.03.2026 (የተሻሻለ: 15:44 08.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሀገራዊ የኃይል ምርት ድርሻ 51 በመቶ ደረሰ
ይህ የተነገረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸሙን ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ባቀረበበት ወቅት ነው።
ግድቡ ግንባታው ተጠናቆ ሥራ መጀመሩን ተከትሎ ሀገራዊ የኃይል ምርት በ36 በመቶ እንዲያድግ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ተጫውቷል ተብሏል።
በተጠቀሰው ጊዜ 20.3 ቴራ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት ታቅዶ 18.3 ቴራ ዋት ሰዓት ኃይል ማሳካት ተችሏል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከጎረቤት ሀገራት የኃይል ሽያጭ እና ዳታ ማይኒንግ 247.7 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዳገኘም አስታውቋል።
ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ በበጀት ዓመቱ አካፋይ 7.1 ቢሊዮን ብር ትርፍ አስመዝግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X