ቻድ በሞሮኮው ንጉሥ መሐመድ ስድስተኛ ስም የተሰየመ መስጂድ መርቃ ከፈተች

ሰብስክራይብ

ቻድ በሞሮኮው ንጉሥ መሐመድ ስድስተኛ ስም የተሰየመ መስጂድ መርቃ ከፈተች

አዲሱ ግዙፍ ህንፃ በ33 ሺህ ስኩዌር ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ከ3 ሺህ በላይ ሰዎችን የማስተናገድ አቅም አለው።

የካቲት 27 በተካሄደው የምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት በንጃሜና የሞሮኮ አምባሳደር አብደላቲፍ ኤሮጃ፤ መስጂዱ የአምልኮ ቦታ ብቻ ሳይሆን የባሕል ተፅዕኖ ማዕከል ሆኖ ያገለግላል ብለዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የቻድ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ሼክ ሂሴን ሀሰን አባከር ለፕሮጀክቱ ላበረከቱት አስተዋጽዖ ከሞት በኋላ የሚሰጥ የክብር ምሥጋና ተችሯቸዋል።

በመስጂዱ ውስጥ በተካሄደው የመጀመሪያው የጁምዓ ሶላት በሞሮኮ እና በቻድ መካከል ስላለው ጥልቅ መንፈሳዊ እና አካዳሚያዊ ትስስር እንዲሁም የ "መሐመድ ስድስተኛ የአፍሪካ ምሁራን ፋውንዴሽን" ተልዕኮ በተለየ መልኩ መነሳቱ ተዘግቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0