ኢራን በናይጄሪያ እና በአውሮፓ ሽብርተኝነትን ትደግፋለች የሚሉ ክሶች 'ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ' ናቸው - የኢራን አምባሳደር

© telegram sputnik_ethiopiaኢራን በናይጄሪያ እና በአውሮፓ ሽብርተኝነትን ትደግፋለች የሚሉ ክሶች 'ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ' ናቸው - የኢራን አምባሳደር
ኢራን በናይጄሪያ እና በአውሮፓ ሽብርተኝነትን ትደግፋለች የሚሉ ክሶች 'ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ' ናቸው - የኢራን አምባሳደር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 07.03.2026
ሰብስክራይብ

ኢራን በናይጄሪያ እና በአውሮፓ ሽብርተኝነትን ትደግፋለች የሚሉ ክሶች 'ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ' ናቸው - የኢራን አምባሳደር

በናይጄሪያ የኢራን አምባሳደር ጎላምሬዛ ማህዳቪ ራጃ፤ ኢራን ራሷ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን ለጎዱ የሽብር ጥቃቶች ለብዙ አስርት ዓመታት ተዳርጋለች ሲሉ ለአንድ የናይጄሪያ የዜና አውታር ተናግረዋል።

አክለውም "እንዲህ ዓይነቱ ውንጀላ [...] የቆየ የጥቃት ታሪክ ባለው እና ዓለም አቀፍ ሕግጋትን በመጣስ በሚታወቀው [የእስራኤል] አገዛዝ የሚካሄድ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ አካል ነው" ብለዋል።

የዜና አውታሩ አምባሳደር ራጃን፤ ናይጄሪያ ኢራን ከአፍሪካ አኅጉር ጋር በምታደርገው ግንኙነት ውስጥ ትልቅ እና ጉልህ ቦታ አላት ማለታቸውን ጠቅሶ ዘግቧል።

"ኢራን ከናይጄሪያ እና ከሁሉም የአፍሪካ ሀገራት ጋር ገንቢ እና ዘላቂ ግንኙነት ትፈልጋለች" ሲሉ አምባሳደሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የእስራኤል አምባሳደር ቀደም ሲል ከሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ቴህራን በናይጄሪያ እና በመላው አውሮፓ ሽብርተኝነትን ትደግፋለች ሲሉ በመክሰስ፤ በኢራን ላይ ለሚሰነዘረው ወታደራዊ ጥቃት በምክንያትነት አቅርበውታል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0