የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ የመካከለኛውን ምስራቅ ቀውስ ተከትሎ የናይጄሪያን የነዳጅ አቅርቦት ለማረጋገጥ ቃል ገባ
19:41 06.03.2026 (የተሻሻለ: 19:44 06.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የዳንጎቴ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካ የመካከለኛውን ምስራቅ ቀውስ ተከትሎ የናይጄሪያን የነዳጅ አቅርቦት ለማረጋገጥ ቃል ገባ
በአሜሪካ-እስራኤል እና በኢራን መካከል ባለው ጦርነት ምክንያት የዓለም የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ እየናረ በመጣበት እና የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካዎች እየተዘጉ ባሉበት በዚህ ወቅት፤ ለናይጄሪያውያን የነዳጅ አቅርቦትን ለማረጋገጥ ለሀገር ውስጥ ገበያ ቅድሚያ እንደሚሰጥ የናይጄሪያው ግዙፍ ኩባንያ በመግለጫው አስታውቋል።
ፋብሪካው በዲፖ መውጫ ዋጋ ላይ ያደረገው መጠነኛ ማስተካከያ ከዓለም አቀፍ ገበያ ነዳጅ መግዛት የቀጠሉ የግል ድርጀቶች የሚከፍሉት መስዋዕትነት መሆኑን ገልጿል።
ዳንጎቴ የሀገር ውስጥ ማጣሪያ ናይጄሪያን ከዓለም አቀፍ የአቅርቦት መቆራረጥና እጥረት ይጠብቃል ብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/