ዚምባብዌ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 2027 ከሀገር በቀል ባለሀብቶች ጋር ካልተጣመሩ እንዲወጡ የሚያዝ አዲስ ገደብ ጣለች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱዚምባብዌ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 2027 ከሀገር በቀል ባለሀብቶች ጋር ካልተጣመሩ እንዲወጡ የሚያዝ አዲስ ገደብ ጣለች
ዚምባብዌ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 2027 ከሀገር በቀል ባለሀብቶች ጋር ካልተጣመሩ እንዲወጡ የሚያዝ አዲስ ገደብ ጣለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.03.2026
ሰብስክራይብ

ዚምባብዌ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 2027 ከሀገር በቀል ባለሀብቶች ጋር ካልተጣመሩ እንዲወጡ የሚያዝ አዲስ ገደብ ጣለች

የፍትሕ ሚኒስትሩ ዚያምቢ ዚያምቢ ለፓርላማ እንደገለጹት፤ በዚምባብዌ ሕጋዊ መመሪያ ቁጥር 215 መሠረት ለዚምባብዌ ዜጎች ብቻ በተፈቀዱ የንግድ ዘርፎች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የውጭ ኩባንያዎች እስከ 2027 ድረስ ከሀገር በቀል ባለሀብቶች ጋር መጣመር አልያም ሥራቸውን አቁመው መውጣት ይኖርባቸዋል።

ሚኒስትሩ የጠቀሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

◻ አዲሱ ደንብ የዜጎችን የኢኮኖሚ ተሳትፎ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን የተወሰኑ የንግድ እንቅስቃሴዎችን ለዚምባብዌ ዜጎች ይከለክላል።

◻ መንግሥት ከኢንዱስትሪ እና ንግድ ሚኒስቴር እንዲሁም ከንግድ ባለድርሻ አካላት ጋር በመካከር የአፈጻጸም ሂደቱን ይገመግማል፡፡

◻ ይህ ፖሊሲ ለኩባንያዎች በቂ የማስተካከያ ጊዜ በመስጠት፤ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ዘርፎችን በዚምባብዌ ዜጎች እጅ ለማስገባት የሚደርገው ሰፊ ጥረት አካል ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0