የኢራን አብዮታዊ ዘብ ጠዋት በአሜሪካ እና የእስራኤል ኢላማዎች ላይ ያካሄደው ድብደባ በትምህርት ቤት ለተፈፀመው ጥቃት የበቀል እርምጃ መሆኑን
17:39 06.03.2026 (የተሻሻለ: 17:44 06.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢራን አብዮታዊ ዘብ ጠዋት በአሜሪካ እና የእስራኤል ኢላማዎች ላይ ያካሄደው ድብደባ በትምህርት ቤት ለተፈፀመው ጥቃት የበቀል እርምጃ መሆኑን
አስታወቀ
የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን የኢራን አብዮታዊ ዘብ መግለጫን ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ "የእውነተኛ ቃል ኪዳን 4" 22ኛ ዙር ጥቃት የተሰነዘረው በሚናብ ትምህርት ቤት ውስጥ የተገደሉ ሕፃናትን ደም ለመበቀል ነው።
ጥቃቶቹ በቴል አቪቭ እና በሃይፋ የሚገኙ የጦር ሠፈሮችን፣ ወታደራዊ ቦታዎችን እና የቤን ጉሪዮን አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ ከፋርስ ባሕረ ሰላጤ እስከ ቴል አቪቭ የአሜሪካ እና የእስራኤል ኢላማዎችን እንደመቱ አስታወቋል።
በጥቃቱ የከይባር ሃይፐርሶኒክ እና የቅርብ ጊዜው የኩራምሻህር ከባድ ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ ውለው ሁሉም ተተኳሾች በተሳካ ሁኔታ ኢላማቸውን መምታታቸውን አብዮታዊ ዘቡ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X