የጤና ሚኒስቴር የፀሐይ ኃይል መሳሪያዎችንና ሞተር ሳይክሎችን ለክልሎች አስረከበ
13:07 06.03.2026 (የተሻሻለ: 13:14 06.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጤና ሚኒስቴር የፀሐይ ኃይል መሳሪያዎችንና ሞተር ሳይክሎችን ለክልሎች አስረከበ
ሚኒስቴሩ 380 የጤና ተቋማት የፀሐይ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችሉ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ መሳሪያዎችን እና 1,183 በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙ ሞተር ሳይክሎችን ለክልል የጤና ቢሮዎች አስረክቧል።
መሳሪያዎቹ የጤና ተቋማት አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ የሚያስችሉና አስቸጋሪ በሆኑ አካባቢዎች ክትባትና መድኃኒት ለማድረስ የሚረዱ መሆናቸውን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ በርክክቡ ላይ ተናግረዋል፡፡
"መንግሥት ለአየር ንብረት ተፅዕኖ የማይበገር የጤና ተቋማትን ለመገንባት እየሠራ ነው" ብለዋል።
ድጋፉ በተለይም በገጠር አካባቢዎች የሚታየውን የጤና አገልግሎት ፍትሐዊነት ክፍተት በመሙላት የእናቶች እና የሕፃናትን ጤና ለማሻሻል ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

