ጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ቦይንግ ጅማን የአፍሪካ የኤሮስፔስ ትምህርት የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል አጋርነት መሠረቱ
18:52 05.03.2026 (የተሻሻለ: 18:54 05.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ እና ቦይንግ ጅማን የአፍሪካ የኤሮስፔስ ትምህርት የልህቀት ማዕከል ለማድረግ የሚያስችል አጋርነት መሠረቱ
ዩኒቨርሲቲው ከግዙፉ የአውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር የተፈራረመው ስምምነት በጅማ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የተቋቋመውን የኢቪዬሽን ሳይንስ እና ኤሮስፔስ ኢንጂነሪንግ አካዳሚ በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የመማሪያ ክፍሎችን ማዘመን፣ የመምህራን ሥልጠና እና የተማሪዎችን የፈጠራ ሥራዎች የሚያበረታታ "የኤሮስፔስ ኢንኖቬሽን ቻሌንጅ" ማካሄድን እንደሚያካትት ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
ቦይንግ በበኩሉ፤ አፍሪካ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ፓይለቶችና ቴክኒሻኖችን ጨምሮ ከ74,000 በላይ አዳዲስ የኢቪዬሽን ባለሙያዎች እንደሚያስፈልጋት በመግለጽ፤ ይህ አጋርነት የአኅጉሪቱን የሰው ኃይል ፍላጎት ይቀርፋል ብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X