በአዲስ አበባ ከሕንዳዊ ዜጋ ስልክ የሰረቁ ተጠርጣሪዎች በዘመናዊ ፖሊስ ጣቢያ በታገዘ ፈጣን እርምጃ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ሰብስክራይብ

በአዲስ አበባ ከሕንዳዊ ዜጋ ስልክ የሰረቁ ተጠርጣሪዎች በዘመናዊ ፖሊስ ጣቢያ በታገዘ ፈጣን እርምጃ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ተበዳዩ ሚስተር ሳንቶስ ኩማር፤ በአካል ፖሊስ ጣቢያ መሄድ ሳያስፈልጋቸው በቅርባቸው የሚገኘውን የሰው አልባ የፖሊስ አገልግሎት በመጠቀም አቤቱታቸውን አቅርበው፤ ፖሊስ ባካሄደው ፈጣን ክትትል ተጠርጣሪዎቹ ተይዘው ስልካቸው ተመልሷል።

"በርካታ ሀገራትን ጎብኝቻለሁ፤ ነገር ግን እንዲህ ያለ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታጠቀና ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የፖሊስ ተቋም አይቼ አላውቅም" ሲሉም አገልግሎቱን አወድሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሰው አልባ ዘመናዊ የፖሊስ ጣቢያ በአዲስ አበባ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0