ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የዓለም አትሌቲክስ ውድድርን ለማስተናገድ ተመረጠች
13:41 05.03.2026 (የተሻሻለ: 13:44 05.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ግዜ የዓለም አትሌቲክስ ውድድርን ለማስተናገድ ተመረጠች
የዓለም አትሌቲክስ አኅጉራዊ ጉብኝት አካል የሆነው የአንድ ቀን ውድድር በመጪው ሚያዝያ 10 2018፤ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ዓለም አቀፉ ተቋም በመርኃ-ግብር ግዜ ማሳወቂያ ሰሌዳው ይፋ አድርጓል፡፡
በውደድሩ ከተለያዩ ሀገራት የተወጣጡ እውቅ አትሌቶች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ውድድሩን ለማስተናገድ መመረጧ አዲስ ምዕራፍ ነው ሲል የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል።
ይህ ዜና የዓለም አትሌቲክስ የውድድር ዋና ዳይሬክተር ፒርስ ኦክላጋን በየካቲት ወር መጀመሪያ በኢትዮጵያ የሁለት ቀን የሥራ ጉብኝት ማድረጋቸውን ተከትሎ የመጣ ነው፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X