48ኛው የካራማራ ጦርነት የድል በዓል ተከበረ
10:34 05.03.2026 (የተሻሻለ: 10:44 05.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
48ኛው የካራማራ ጦርነት የድል በዓል ተከበረ
መታሰቢያ በዓሉ አዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮ-ኩባ የወዳጅነት ፓርክ የቀድሞው ጦር ሠራዊት አባላት፣ የኢትዮ-ኩባ ወዳጅነት ማኅበር አባላት እንዲሁም በኢትዮጵያ የኩባ አምባሳደር ሜይሊን ሱአሬዝ አልቫሬዝና ሌሎችም በተገኙበት በመከበር ላይ ይገኛል።
ኩባ በውጊያው ከኢትዮጵያ ጋር በመቆም 18 ሺህ በላይ እግረኛና ሜካናይዝድ ጦር ድጋፍ እንዳደርገች ይነገራል፡፡
ቀኑ፤ የካቲት 26፣ 1970 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጦር ወራሪውን የሶማሊያ ሠራዊት ድል በማድረግ ካራማራ ተራራ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ያውለበለበበት ታሪክ የሚታወስበት ነው፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

