የኢትዮ ቴሌኮም ጨምሮ የስድስት የአፍሪካ የቴሌኮም ኩባንያ አመራሮች በባርሴሎና የሞባይል ወርልድ ኮንግረስ የመጀመሪያውን የአፍሪካ ፓቪሊዮን መረቁ
19:03 04.03.2026 (የተሻሻለ: 19:04 04.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮ ቴሌኮም ጨምሮ የስድስት የአፍሪካ የቴሌኮም ኩባንያ አመራሮች በባርሴሎና የሞባይል ወርልድ ኮንግረስ የመጀመሪያውን የአፍሪካ ፓቪሊዮን መረቁ
በኢትዮ ቴሌኮም ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ሐሳብ አመንጪነት የተከፈተው ማሳያ፣ በዓለም ግዙፉ የሞባይል ኢንዱስትሪ ኮንፈረንስ ታሪክ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከናወነ ታሪካዊ ሁነት መሆኑን ኩባንያው ገልጿል፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚዋ እንዳብራሩት ስትራቴጂያዊ ጥምረቱ፡-
የዲጂታል አገልግሎት አጠቃቀም ክፍተትን ለማጥበብ፣
አካታች የገጠር የቴሌኮም ተደራሽነትን ለማረጋገጥ፣
ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸውን ስማርት ስልኮች ማቅረብ እና
የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ማስፋፋት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡
በተለይም፣ በአፍሪካ ነባራዊ ሁኔታ ላይ ያተኮሩ አፍሪካ-ተኮር ብዝሃ የቋንቋ ሞዴሎችን ማበልጸግ፣ አኅጉሪቱ ለሰው ሠራሽ አስተውሎት ያላትን ዝግጁነት ለማረጋገጥና የዲጂታል ሉዓላዊነቷን ለማጠናከር ልዩ ትኩረት እንደሚሰጠው በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ተገልጿል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/2
© telegram sputnik_ethiopia

2/2
© telegram sputnik_ethiopia
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
2/2
© telegram sputnik_ethiopia