ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ የመከላከያ እና የሰው ሠራሽ አስተውሎት ትብብራቸውን አጠናከሩ
17:49 04.03.2026 (የተሻሻለ: 17:54 04.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ሩዋንዳ የመከላከያ እና የሰው ሠራሽ አስተውሎት ትብብራቸውን አጠናከሩ
የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ ከሩዋንዳ መከላከያ ቃል አቀባይ ብርጋዴር ጄኔራል ሮናልድ ሪቪዋንጋ ጋር በሃገራቱ መካከል ያለውን የቆየ የሁለትዮሽ ትብብር በተለይም በመከላከያ ዘርፍ ይበልጥ ለማጠናከር ተወያይተዋል፡፡
ሁለቱም ወገኖች የተግባር ቅልጥፍናን፣ የደህንነት መረጃ ትንተናን እና ስትራቴጂካዊ ዝግጁነትን ለማሳደግ የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የላቁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የመከላከያ ትብብሩን ከዘመናዊ የደህንነት ተግዳሮቶች ጋር ማላመድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
አይሻ መሐመድ፣ ኢትዮጵያ ከሩዋንዳ ጋር በፈጠራ የታገዙ የመከላከያ ተነሳሽነቶች ላይ ያለውን ትብብር ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን በድጋሚ አረጋግጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X