በኒውክሌር መሣሪያ የማስፈራራት ስልት አሁንም ‘የዓለም አቀፍ ደህንነት የማዕዘን ድንጋይ’ ሆኖ ቀጥሏል - ክሬምሊን
16:07 04.03.2026 (የተሻሻለ: 16:14 04.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኒውክሌር መሣሪያ የማስፈራራት ስልት አሁንም ‘የዓለም አቀፍ ደህንነት የማዕዘን ድንጋይ’ ሆኖ ቀጥሏል - ክሬምሊን
በስትራቴጂካዊ ዓለም አቀፍ የደህንነት መዋቅር ላይ የሚደረጉ ቀጣይ ውይይቶች የአውሮፓ የኒውክሌር ኃይሎችን ማካተት አለባቸው ሲሉ የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው ያነሷቸው ሌሎች ዋና ዋና ነጥቦች፦
ኢራን ካለችበት ሁኔታ አንጻር፣ የአውሮፓ አገራት ሩሲያ የኃይል አቅርቦትን እንድትቀጥል ወይም እንድትጨምር አልጠየቁም።
የሩሲያን ነዳጅ የሚገዙት ሃንጋሪ እና ስሎቫኪያ በኪዬቭ የማስፈራራት ድርጊት እየገጠማቸው ነው።
ፑቲን በዛሬው ዕለት በሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር የቦርድ ስብሰባ ላይ እንዲሳተፉ፣ የካቢኔ ስብሰባ እንዲያካሂዱ እና በክሬምሊን ከሃንጋሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር እንዲገናኙ መርሃ ግብር ተይዞላቸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X