በመካከለኛው ምስራቅ ያለው የግጭት መባባስ ስጋት፦ 'ድብቅ ተዋናዮች' ሊመጡ ይችላሉ ሲሉ ሳይንቲስቱ ተናገሩ

ሰብስክራይብ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው የግጭት መባባስ ስጋት፦ 'ድብቅ ተዋናዮች' ሊመጡ ይችላሉ ሲሉ ሳይንቲስቱ ተናገሩ

​ይህንን ግጭት ወደ ዓለም አቀፋዊ ደረጃ የማደግ ዕድል እንዳለው፣ የ"ወርልድ አድቫንስድ ሪሰርች ፕሮጀክት ኤጀንሲ" ዋና ሥራ አስፈፃሚ እና የቀድሞው የኢኤዲኤስ/ኤርባስ ግሩፕ ሳይንሳዊ ዳይሬክተር ዣን ፍራንኮይስ ጄኔስት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

​"በርካታ ሁኔታዎች ሊፈጠሩ ይችላሉ። ለምሳሌ ፈረንሳይ ሚና ሊኖራት ይችላል፤ ምናልባትም እንግሊዝና እና ጀርመን። በምዕራባውያን በኩል በኢራን ላይ እየጨመረ የመጣውን የኃይል አለመመጣጠን ተከትሎ የግጭቱ መባባስ ልናይ እንችላለን። ቀስ በቀስም ቻይና እና ሩሲያ የኃይል ሚዛኑን ለመጠበቅ ጣልቃ ለመግባት ሊወስኑ ይችላሉ።"

​እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ኢራን አጸፋዊ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስፈልጋት ትጥቅ አላት፤ በተለይም፦

​▪ ከአሜሪካ የባሕር ዳርቻዎች ብዙም ሳይርቁ ሊቀመጡ የሚችሉ የባሕር ሰርጓጅ መርከቦች፤

▪ አሜሪካን ለመድረስ የሚሞክሩ የሚችሉ ባለስቲክ ሚሳኤሎች።

​"ኢራን የአሜሪካን አቅም በድንገተኛ ጥቃት ለማሽመድመድ፣ በአቅራቢያ የሚገኙትን አንዱን ወይም ሁለቱንም የአውሮፕላን ተሸካሚ መርከቦች ማውደም ትችል ነበር። ነገር ግን ያኔ የአጸፋዊ እርምጃው ጥያቄ ይነሳል" ሲሉ ባለሙያው አፅንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0