ከ2.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የኢንቨስትመት ስምምነት ለመፈራረም አቅደናል - የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን

ሰብስክራይብ

ከ2.4 ቢሊዮን ዶላር በላይ  የኢንቨስትመት ስምምነት ለመፈራረም አቅደናል - የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን

በ4ተኛው ዙር "በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ" ፎረም ኢትዮጵያ ያላትን ዕምቅ የኢንቨስትመንት አቅም ከማስተዋወቅ ባሻገር፤ ከ2.4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የኢንቨስትመንት ስምምነት ለመፈራረም መታቀዱን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን (ዶ/ር) ተናግረዋል።

ኮሚሽነሩ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ "በሦስተኛው ዙር 1.6 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚያወጣ ስምምነት መፈረም ችለናል። በወቅቱ ከኮሚሽን ጋር ስምምነት የተፈራረሙት ባለሐብቶች በሙሉ ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ መላክ ጀምረዋል።" ብለዋል።

አራተኛው ዙር "በኢትዮጵያ ኢንቨስት ያድርጉ ፎረም መጋቢት 17 እና 18 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0