የኢራን የመቋቋም አቅም እና ያልተመጣጠነ ስልት የአሜሪካን ጥምረት ለምን አስገረመ?

የኢራን የመቋቋም አቅም እና ያልተመጣጠነ ስልት የአሜሪካን ጥምረት ለምን አስገረመ?
የቀድሞው የስዊድን ጦር ኃይል እና የአየር መከላከያ መኮንን ሚካኤል ቫልተርሰን ለስፑትኒክ እንደተናገሩት፣ ኢራን የ12 ቀኑን የጦርነት ትምህርቶች በሚገባ ተረድታለች።
"ከ12 ቀኑ ጦርነት የተገኘው ትልቁ ትምህርት ከአደጋ መተርፍ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ነው። የጠላት ከፍተኛ ድብደባ ቢኖርም ሊተርፍ የሚችል የዕዝ መዋቅር እና የጦር መሣሪያ አቅም ሊኖር ይገባል" ሲሉ ቫልተርሰን አስረድተዋል።
ባለሙያው ኢራን እንዲህ ዓይነቱን የመቋቋም አቅም እንዳሳየች ይሞግታሉ። አመራሯ እና የታጠቀው ኃይሏ አሁንም በሥራ ላይ ሲሆኑ፣ ከፍተኛ መጠን ያለው የአጸፋ ጥቃት የመሰንዘር አቅም አላቸው።
ባለፈው ዓመት ሰፊ የሞሳድ መረቦች መፈራረሳቸው እና በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የተቃዋሚ መሪዎች መወገዳቸው የኢራንን የውስጥ መረጋጋት የበለጠ አጠናክሮታል።
የረጅም ጊዜ ጦርነት፣ ኢራን የአሜሪካ እና የእስራኤልን ድንገተኛ የፈጣን ድል ጥቃት ወደ ረጅም ጊዜ አድካሚ ጦርነት መለወጥ የቻለች ይመስላል።
የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን፣ ኢራን አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ካደረገችው መስፋፋት እና በዩክሬን ካለው ግጭት ትምህርቶችን መውሰዷን አምነዋል፡፡
"የሞዛይክ መከላከያ"፣ ኢራን ማዕከል መር ያልሆነ እና በተለያዩ "ሴሎች" (የቦታ ምድቦች) የተከፋፈሉ ወታደራዊ ክፍሎችን አሰማርታለች። እነዚህ ክፍሎች የአሜሪካ እና የእስራኤልን ከፍተኛ አመራሮችን የማጥፋት ስልት ለመመከት ታስበው የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከሰፊ ግዛቷ ውስጥ ድንገተኛ የድሮን እና ሚሳኤል ጥቃቶችን መሰንዘር ይችላሉ።
መጠነ -ሰፊ የድሮን ጥቃት፣ የጠላትን የአየር መከላከያ ለማጨናነቅ እና የአሜሪካንና የአጋሮቿን የሚሳኤል ክምችት ለማሟጠጥ ታስቦ የተዘጋጀ፣ የተቀናጀ የድሮን ጥቃት እና የሚሳኤል ጥቃቶችን በስፋት እየተጠቀመች ትገኛለች።
የኢራን የአጸፋ ጥቃቶች
እንደ ባለሙያው ገለጻ፣ ኢራን በባሕረ ሰላጤው በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ ጉዳት ለማድረስ የቻለችው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
ቅርበት፦ ለኢራን ቅርብ መሆናቸው የማስጠንቀቂያ ጊዜን በጣም አጭር ያደርገዋል።
ደካማ ቅንጅት፦ በአሜሪካ ጦር እና በአካባቢው አጋሮች መካከል ያለው ደካማ ቅንጅት የጦር ሰፈሮቹን መከላከያ ያዳክማል።
የሀብት ክፍፍል፦ ዋና ዋና የአሜሪካ የአየር መከላከያ መሣሪያዎች እስራኤልን ለመጠበቅ ተጠምደዋል።
የራዳር መውደም፦ ኢራን ቀደም ብላ የአሜሪካን ኤኤን/ኤፍፒኤስ -132 የተባለውን የረጅም ርቀት ራዳር በማውደሟ፣ አሜሪካ የሚሳኤል ጥቃቶችን የመለየት አቅሟ ተገድቧል።
"በአጠቃላይ፣ የኢራን ዓላማ የጠላትን የአየር መከላከያ ክምችት ማሟጠጥ፣ ይህ በሚሆንበት ጊዜ የመምታት አቅምን ጠብቆ ማቆየት፣ ለአሜሪካ የሚወጣውን የኢኮኖሚ ወጪ መጨመር እና በእርግጥም ከጥቃቱ ተርፎ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫናው ሊቋቋሙት ከሚችሉት በላይ እስኪሆን ድረስ አሜሪካን ጦርነቱን እንድታቆም ማስገደድ ነው።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X