በኢትዮጵያ ባንኮች መካከል በተካሄደ ሳምንታዊ ገበያ የአንድ ጀምበር ግብይት 87.4 ቢሊዮን ብር በመድረስ አዲስ ታሪክ አስመዘገበ
17:54 03.03.2026 (የተሻሻለ: 18:04 03.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ ባንኮች መካከል በተካሄደ ሳምንታዊ ገበያ የአንድ ጀምበር ግብይት 87.4 ቢሊዮን ብር በመድረስ አዲስ ታሪክ አስመዘገበ
ይህ ከየካቲት 16 እስከ 20 ባሉት ቀናት ውስጥ የተመዘገበ አሃዝ፣ በ125 የአንድ ጀምበር የገንዘብ ልውውጥ ስምምነቶች አማካኝነት የተፈፀመ ነው።
የገንዘብ እንቅስቃሴው ባንኮች የአጭር ጊዜ የጥሬ ገንዘብ ፍላጎታቸውን የሚያስተዳድሩበት መንገድ ላይ የታየ ፈጣን ለውጥን ያሳያል።
የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ ይህ ሳምንታዊ የግብይት መጠን ቀደም ሲል በጥር ወር ተመዝግቦ የነበረውን የ53 ቢሊዮን ብር ከፍተኛ ክብረ ወሰንን በሰፊ ልዩነት በልጧል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ይህ ድንገተኛ ጭማሪ የገብይት መድረኩ ከተጀመረ አንስቶ ያለውን አጠቃላይ የግብይት መጠን ወደ 1.96 ትሪሊዮን ብር ከፍ አድርጎታል። ይህም ገበያው ወደ ሁለት ትሪሊዮን ብር ጣሪያ ለመድረስ መቃረቡን ያሳያል ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X