የሩዋንዳ ጦር በምስራቅ ኮንጎ ግጭት ውስጥ ባለው ሚና ምክንያት በአሜሪካ ማዕቀብ ተጣለበት
17:27 03.03.2026 (የተሻሻለ: 17:34 03.03.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩዋንዳ ጦር በምስራቅ ኮንጎ ግጭት ውስጥ ባለው ሚና ምክንያት በአሜሪካ ማዕቀብ ተጣለበት
የአሜሪካ የግምጃ ቤት እንዳስታወቀው፣ የኤኤፍሲ/ኤም23 አማጺ ቡድን በምስራቅ ኮንጎ እያደረገ የሚገኘው የግዛት መስፋፋት "ያለ ሩዋንዳ ድጋፍ የማይታሰብ" ነው ብሏል።
ቁልፍ ነጥቦች፦
🟠 ማዕቀቦቹ፦ በሩዋንዳ መከላከያ ኃይል እና ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናት ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። ከእነዚህም መካከል የጦር ኃይሉ የጥናትና እቅድ ሹም፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እንዲሁም የልዩ ዘመቻ እና የባህር ኃይል ክፍለ ጦር አዛዦች ይገኙበታል።
🟠 የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ምላሽ፦ ኪንሻሳ የተወሰደውን እርምጃ የደገፈች ሲሆን፣ "ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት መከበር ጠንካራ ምልክት ነው" ስትል ገልጻዋለች።
🟠 የሩዋንዳ ምላሽ፦ ኪጋሊ በበኩሏ ማዕቀቡን ውድቅ አድርጋለች። ማዕቀቡ "እውነታውን ያዛባ ነው" ያለች ሲሆን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለታጣቂ ቡድኖች የምታደርገውን ድጋፍ ለማቆም የገባችውን ቃል አልጠበቀችም ስትል ከሳለች።
በምስራቅ ኮንጎ ሰሜን ካባሬ አካባቢ በኮንጎ ጦር እና በኤም23 አማፂያን መካከል በሚካሄደው ግጭት ወቅት ተማሪዎች ተሸሽገው የሚያሳይ የቆየ ቪዲዮ
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X