የሩዋንዳ ጦር በምስራቅ ኮንጎ ግጭት ውስጥ ባለው ሚና ምክንያት በአሜሪካ ማዕቀብ ተጣለበት

ሰብስክራይብ

የሩዋንዳ ጦር በምስራቅ ኮንጎ ግጭት ውስጥ ባለው ሚና ምክንያት በአሜሪካ ማዕቀብ ተጣለበት

​የአሜሪካ የግምጃ ቤት እንዳስታወቀው፣ የኤኤፍሲ/ኤም23 አማጺ ቡድን በምስራቅ ኮንጎ እያደረገ የሚገኘው የግዛት መስፋፋት "ያለ ሩዋንዳ ድጋፍ የማይታሰብ" ነው ብሏል።

ቁልፍ ነጥቦች፦

​🟠 ማዕቀቦቹ፦ በሩዋንዳ መከላከያ ኃይል እና ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናት ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። ከእነዚህም መካከል የጦር ኃይሉ የጥናትና እቅድ ሹም፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እንዲሁም የልዩ ዘመቻ እና የባህር ኃይል ክፍለ ጦር አዛዦች ይገኙበታል።

​🟠 የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ምላሽ፦ ኪንሻሳ የተወሰደውን እርምጃ የደገፈች ሲሆን፣ "ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት መከበር ጠንካራ ምልክት ነው" ስትል ገልጻዋለች።

​🟠 የሩዋንዳ ምላሽ፦ ኪጋሊ በበኩሏ ማዕቀቡን ውድቅ አድርጋለች። ማዕቀቡ "እውነታውን ያዛባ ነው" ያለች ሲሆን፣ ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ለታጣቂ ቡድኖች የምታደርገውን ድጋፍ ለማቆም የገባችውን ቃል አልጠበቀችም ስትል ከሳለች።

በምስራቅ ኮንጎ ሰሜን ካባሬ አካባቢ በኮንጎ ጦር እና በኤም23 አማፂያን መካከል በሚካሄደው ግጭት ወቅት ተማሪዎች ተሸሽገው የሚያሳይ የቆየ ቪዲዮ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0