ሞዛይክ መከላከያ፡- ኢራን ከፍተኛ አመራሮቿን ኢላማ ካደረገ ጥቃት ትታደግ ዘንድ የዋለ ስትራቴጂካዊ ዋስትና

© telegram sputnik_ethiopiaሞዛይክ መከላከያ፡- ኢራን ከፍተኛ አመራሮቿን ኢላማ ካደረገ ጥቃት ትታደግ ዘንድ የዋለ ስትራቴጂካዊ ዋስትና
ሞዛይክ መከላከያ፡- ኢራን ከፍተኛ አመራሮቿን ኢላማ ካደረገ ጥቃት ትታደግ ዘንድ የዋለ ስትራቴጂካዊ ዋስትና - Sputnik አፍሪካ, 1920, 02.03.2026
ሰብስክራይብ

ሞዛይክ መከላከያ፡- ኢራን ከፍተኛ አመራሮቿን ኢላማ ካደረገ ጥቃት ትታደግ ዘንድ የዋለ ስትራቴጂካዊ ዋስትና

​የሩሲያ ወታደራዊ ታዛቢ ኢጎር ኮሮትቼንኮ ለስፑትኒክ እንደገለጹት፣ ሞዛይክ መከላከያ ማለት "የታጠቀው ኃይል ዕዝ እና ቁጥጥር የተማከለ ሳይሆን ተበታትኖ እንዲዋቀር የሚያደርግ፣ እንዲሁም አስቀድሞ በተቀረጸ ዕቅድ መሠረት አስቀድሞ በተለዩ ኢላማዎች ላይ ጥቃት የሚሰነዘርበት ሥርዓት ነው" ብለዋል።

​"የኢራን ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አመራሮች በመጀመሪያው ጥቃት አንዳንዶቹ ሊገደሉ እንደሚችሉ አስቀድመው መገመታቸው ግልጽ ነው። ስለዚህ የኢራን አብዮታዊ ዘብ እና የኢራን ጦር የሚሰነዝሩት የሚሳኤል ጥቃት በተቻለ መጠን ውጤታማ እንዲሆን፤ ዕቅዶች አስቀድመው ተዘጋጅተዋል፣ አስፈላጊ ሀብቶችም ተመድበዋል" ሲሉ የሩሲያ ብሔራዊ መከላከያ መጽሔት ዋና አዘጋጅ ኮሮትቼንኮ አስረድተዋል።

​ኮሮትቼንኮ አክለውም፣ ኢራን ከእሷ በላቀ ወታደራዊ አቅም ካለው ተቃዋሚ ጋር ረጅም ጊዜ የሚቆይ ጦርነት ለማካሄድ የምትችልበት "ብቸኛው መንገድ" ይህ የሞዛይክ መከላከያ ስትራቴጂ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል።

​ይህ ስትራቴጂ ከቅዳሜው የአሜሪካ እና የእስራኤል ድንገተኛ ጥቃት በኋላ ምን ያህል ዋጋ ያለው እንደሆነ ያስመሰከረ ሲሆን፣ ዋናው ጥቅሙም "የኢራን ከፍተኛ መሪዎች ቢገደሉ እና የአየር መከላከያዋ በጥቃት ቢዳከም እንኳ የጦር ተቃውሞን የመቀጠል አቅም" መሆኑ ተገልጿል።

​አሁን ያለው የኢራን ጥቃት ጥንካሬ ከቀጠለ፣ "ለተቃዋሚዎቿ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ፣ አልፎ ተርፎም በአንዳንድ ሁኔታዎች ወሳኝ ሊሆን ይችላል" ብለዋል ተንታኙ።

"ኢራን የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ወይም የጋራ የኢኮኖሚ ፕሮጀክቶች ባሏቸው ሀገራት ላይ የነበራትን ማንኛውንም ቀይ መስመር በግልጽ ትታለች" ሲሉ ኮሮትቼንኮ ገልጸዋል። ወታደራዊ ተቋማትን ኢላማ ካደረገች በኋላ፣ አሁን "የባህረ ሰላጤው ሀገራት መሠረተ ልማት ላይ ስልታዊ ጥቃት በመሰንዘር አሜሪካን ከተጨማሪ ጥቃት እንዲያግዱ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ጫና እንዲፈጥሩ ታደርጋለች" ብለዋል።

​"አሁን ያለው ዋናው ጥያቄ የኢራን አየር መከላከያ ጽናት እና የአሜሪካንና የእስራኤልን የአየር ጥቃቶች የመቋቋም አቅም ነው"።

  "በአሁኑ ወቅት በጣም ወሳኝ በሆነ የሁነቶች ምዕራፍ ላይ እንገኛለን። በሚቀጥሉት 5-7 ቀናት ውስጥ ምን እንደሚፈጠር እናያለን፤ እነሱም የወደፊቱን አቅጣጫ ያሳያሉ። ለጊዜው የኢራን የውስጥ ፖለቲካ ሁኔታ የተረጋጋ ሲሆን፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ የተበታተነ የቁጥጥር ሞዴል ጥቅሙን እያሳየ ነው፤ ይህም ትራምፕም ሆኑ ኔታንያሁ የጠበቁት አይመስልም" ሲሉ ኮሮትቼንኮ ንግግራቸውን አጠቃለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0