ናይጄሪያ ከአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ጋር የ1.3 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራረመች
16:10 02.03.2026 (የተሻሻለ: 16:14 02.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ ከአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ጋር የ1.3 ቢሊዮን ዶላር የኢንቨስትመንት ስምምነት ተፈራረመች
በጠጣር ማዕድናት ልማት ፈንድ በኩል የተፈረመው ይህ ስምምነት የሚከተሉትን ያካትታል፦
የአሉሚኒየም ማጣሪያ መገንባት፣
ብሔራዊ የማዕድን ካርታ ሥራ ፕሮግራም መጀመር፣
የማዕድን ፍለጋ ሥራን ለማፋጠን የሚያስችል የኢንቨስትመንት ተቋም ማቋቋም የሚሉ ናቸው።
የማዕድን ሚኒስትሩ ደሌ አላኬ እንደገለጹት፣ ማጣሪያው በየዓመቱ 1 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ቦክሳይት የማቀነባበር አቅም ይኖረዋል። በጋዝ ኃይል በሚሠራው በዚህ ፋብሪካ በ20 ዓመታት ውስጥ 19 ሚሊዮን ቶን አሉሚኒየም ለማምረት የታቀደ ሲሆን፣ ይህም በ95 በመቶ የማምረት አቅም ላይ ተመስርቶ የተሰላ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X