"ዓድዋ ለአፍሪካ እና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ጎህ የፈነጠቀ ሰብአዊ ክብርና ሞገስ በዓለም አደባባይ ያበሰረ ታሪካዊ ገድል ነው" ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

ሰብስክራይብ

"ዓድዋ ለአፍሪካ እና ለመላው ጥቁር ህዝብ የነፃነት ጎህ የፈነጠቀ ሰብአዊ ክብርና ሞገስ በዓለም አደባባይ ያበሰረ ታሪካዊ ገድል ነው" ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

በዛሬው ዕለት በመከበር ላይ በሚገኘው 130ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በዓል ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ታዬ፣ ዓድዋ የኢትዮጵያውያን ኍልቈ መሳፍርት ጀግንነት የታየበት በዓል መሆኑን አስረድተዋል።

"ገድሉ የወንዶች ጀግኖች ውሎ ብቻ ሳይሆን ይልቁንም ኢትዮጵያዊት ሴቶች የፖለቲካ መላና ብርቱነት፣ ስትራቴጂያዊ መሪነት እና የሀገር ፍቅር ፅናት ለዓለም የገለፀ የታሪክ ምእራፍ ነው" ሲሉም በድሉ ላይ የኢትዮጵያን ሴቶች ሚና አፅንኦት ሰጥተውበታል።

የዓድዋ ጀግንነት፣ ለኢትዮጵያ የፖለቲካና ዲሞክራሲ ልምምድ እንደ ዋነኛ መተለሚያና መቃኛ ሊያገለግል እንደሚገባ ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል።

"ዓድዋ አጉራጭ ፖለቲካን ይጠየፋል። ጠብ አጫሪዎችንና መከፋፈልን ልማድና ጉርስ ያደረጉትን ያጫምታል። ሌብነትን፣ ውስልትናንና ሃኬትን ይንቃል። የዘመኑ የዓድዋ አረዳድ ቁልፉ ጉዳይ ይሄ ነው" ሲሉም ንግግራቸውን ደምድመዋል።



ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0