'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ
'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.03.2026
ሰብስክራይብ

'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ

​የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለዘ አትላንቲክ እንደተናገሩት፣ የኢራን መሪዎች ድርድር ለመቀጠል እየፈለጉ ሲሆን እርሳቸውም ለመነጋገር ተስማምተዋል።

​“መነጋገር ይፈልጋሉ፤ እኔም ለመነጋገር ተስማምቻለሁ፤ ስለዚህ አነጋግራቸዋለሁ። ይህንን ቀደም ብለው ማድረግ ነበረባቸው። በጣም ቀላል እና ተግባራዊ የነበረውን ነገር ቀደም ብለው መስጠት ነበረባቸው። በጣም ዘገዩ፣” ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።

​ንግግሩ ዛሬ ወይስ ነገ ይካሄዳል ተብለው ሲጠየቁ፣ “ያንን ልነግርህ አልችልም” ሲሉ መልሰዋል።

​ ትራምፕ ቀደም ሲል፣ በድርድሩ ላይ ተሳትፎ የነበራቸው አንዳንዶቹ የኢራን ባለሥልጣናት አሁን በሕይወት እንደሌሉም ጠቁመዋል። “አብዛኞቹ እነዚያ ሰዎች የሉም፤ አብረናቸው ስንገናኝ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች የሉምምክንያቱም ያ ትልቅ ትልቅ ድብደባ ነበር፣” ብለዋል፡፡

ስምምነት ሊያደርጉ ይችሉ ነበር። ቀደም ብለው ማድረግ ነበረባቸው። በጣም ‘ብልጥ’ ለመሆን ሞክረዋል” ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0