'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ
19:57 01.03.2026 (የተሻሻለ: 20:04 01.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
'ለመነጋገር ተስማምቻለሁ' - ትራምፕ ከኢራን ጋር ድርድር ሊቀጥል እንደሚችል ፍንጭ ሰጡ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለዘ አትላንቲክ እንደተናገሩት፣ የኢራን መሪዎች ድርድር ለመቀጠል እየፈለጉ ሲሆን እርሳቸውም ለመነጋገር ተስማምተዋል።
“መነጋገር ይፈልጋሉ፤ እኔም ለመነጋገር ተስማምቻለሁ፤ ስለዚህ አነጋግራቸዋለሁ። ይህንን ቀደም ብለው ማድረግ ነበረባቸው። በጣም ቀላል እና ተግባራዊ የነበረውን ነገር ቀደም ብለው መስጠት ነበረባቸው። በጣም ዘገዩ፣” ሲሉ ትራምፕ ተናግረዋል።
ንግግሩ ዛሬ ወይስ ነገ ይካሄዳል ተብለው ሲጠየቁ፣ “ያንን ልነግርህ አልችልም” ሲሉ መልሰዋል።
ትራምፕ ቀደም ሲል፣ በድርድሩ ላይ ተሳትፎ የነበራቸው አንዳንዶቹ የኢራን ባለሥልጣናት አሁን በሕይወት እንደሌሉም ጠቁመዋል። “አብዛኞቹ እነዚያ ሰዎች የሉም፤ አብረናቸው ስንገናኝ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች የሉም፤ ምክንያቱም ያ ትልቅ ትልቅ ድብደባ ነበር፣” ብለዋል፡፡
“ስምምነት ሊያደርጉ ይችሉ ነበር። ቀደም ብለው ማድረግ ነበረባቸው። በጣም ‘ብልጥ’ ለመሆን ሞክረዋል” ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X