የሩሲያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለኢራን አፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ
19:10 01.03.2026 (የተሻሻለ: 19:14 01.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ለኢራን አፋጣኝ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ጥሪ አቀረቡ
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላህ ቢን ዛይድ አል ናህያን በኢራን ላይ እየተካሄደ ስላለው ጦርነት በስልክ መወያየታቸውን የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል። ሚኒስትሮቹ ውጊያው በአስቸኳይ መቆም እንዳለበትም አሳስበዋል።
ከሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጡ ዋና ዋና መግለጫዎች፦
🟠 ላቭሮቭ አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሚፈጽሙት ጥቃት ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ገልጸዋል።
🟠 ሁለቱም ሚኒስትሮች አፋጣኝ የተኩስ አቁም አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት ሰጥተዋል።
🟠 በአሜሪካ እና በእስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው የቅርብ ጊዜ ጦርነት ቀጣናውን የሚያናጋ መሆኑን ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X