የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሙዚየም በይፋ ተመረቀ
17:59 01.03.2026 (የተሻሻለ: 18:04 01.03.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሙዚየም በይፋ ተመረቀ
ሙዚየሙን መርቀው የከፈቱት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ "የሠራዊት ሙዚየም ለመገንባት የታቀደው ከረጅም ጊዜ በፊት ቢሆንም ጊዜውን ጠብቆ አሁን መሠራቱ ደስ የሚያሰኝ ተግባር ነው፡፡" ብለዋል፡፡
አፈ- ጉባኤው፣ ኢትዮጵያዊያን ከአድዋ ድል አንድነትን፣ ጀግንነትን፣ ነፃነትን ቀስመን አኩሪ ታሪካችንን በመዘከር የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የነገን ብሩህ ተስፋ እናስቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የመከላከያ ሙዚየምና ቅርስ ጥናት አስተዳደር ዳይሬክተር ሜጄር ጄኔራል ጥሩዬ አሰፌ በበኩላቸው፣ ሙዚየሙ የሀገርን ታሪክ ሰንዶ የያዘና ለትዉልዱ አኩሪ ታሪክን የሚዘክር በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገለገልበት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሙዚየ፣ 130ኛውን የአድዋ ድል በዓል መታሰቢያን ምክንያት በማድረግ ለ7 ቀናት ለጎብኚዎች ክፊት ሆኖ ይቆያል ሲል ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

