ኢትዮጵያ የቡና ምርት ላይ ዕሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መመሪያ አስተዋወቀች
18:21 28.02.2026 (የተሻሻለ: 18:24 28.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቡና ምርት ላይ ዕሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አዲስ መመሪያ አስተዋወቀች
መመሪያው የኢትዮጵያ ቡና በሌላ ሀገር ስም እንዳይሸጥና ተፈጥሯዊ ጣዕሙን ጠብቆ ለዓለም ገበያ በማቅረብና የውጭ ምንዛሬ ገቢን በማሳደግ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው የሀገር ውስጥ ሚዲያ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን ኃላፊን ጠቅሶ ዘግቧል።
ይህ አዲስ የፖሊሲ አቅጣጫ፤ ኢትዮጵያ ጥሬ ቡና ከመላክ ወጥታ በሀገር ውስጥ የተቆላና የተፈጨ ቡናን ለዓለም ገበያ እንድትሸጥ የሚያስችል ነውም ተብሏል፡፡
የዘርፉ ባለሙያዎች የቡና መገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ "ከጥቁሩ ወረቅ" ይበልጥ ተጠቃሚ እንድትሆን፤ እሴት በመጨመር ለዓለም ገበያ ማቅረብ እንደሚኖርባት በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X