በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሩድን ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጋር የዓድዋ ድል በዓልን አከበረ
16:33 28.02.2026 (የተሻሻለ: 16:44 28.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከሩድን ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጋር የዓድዋ ድል በዓልን አከበረ
በዝግጅቱ ላይ ንግግር ያደረጉት አምባሳደር ገነት ተሾመ፤ በጦርነቱ ወቅት በሩሲያ ቀይ መስቀል ስር ሩሲያውያን የሕክምና በጎ ፈቃደኞች የቆሰሉ የዓድዋ ተዋጊዎችን በማከም የተጫወቱት ሚና ለሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት መጣሉን አንስተዋል ሲል ኤምባሲው አስታውቋል።
በበዓሉ ላይ የተገኙት የሩድን ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ከፍተኛ ባለሙያ ኢካቴሪና ጉዋፔቶንካ በበኩላቸው፤ ለኢትዮጵያ የተማሪዎች ማኅበረሰብ እና ለኤምባሲው ሠራተኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አከባበሩ በባሕላዊ የቡና ሥነ-ሥርዓት፣ ባሕላዊ ሙዚቃ እና የዳንስ ትርዒት የደመቀ እንደነበር ኤምባሲው ጨምሮ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia

1/2
© telegram sputnik_ethiopia

2/2
© telegram sputnik_ethiopia
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
2/2
© telegram sputnik_ethiopia