አፍሪካ መንቃት እና ራሷ ላይ መሥራት መጀመር አለባት - ታንዛኒያዊ ሥራ ፈጣሪ
19:41 27.02.2026 (የተሻሻለ: 19:44 27.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አፍሪካ መንቃት እና ራሷ ላይ መሥራት መጀመር አለባት - ታንዛኒያዊ ሥራ ፈጣሪ
የአፍሪካ ኢንዱስትሪ የወደፊት ተስፋ ዕድሎችን ወደ ውጭ በመላክ ሳይሆን እሴት መጨመር ላይ ያረፈ እንደሆነ የኬይፒ ሞተርስ መሥራች እና ፕሬዝዳንት መስዑድ ኪፓንያ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
አንድ ፋብሪካ መገንባት የራሱን ሥነ-ምህዳር ይፈጥራል፤ ለአንድ መኪና ብቻ ከተለያዩ አቅራቢዎች የሚመጡ መለዋወጫዎች መፈለጋቸው የሥራ ትስስርን፣ ሽርክናን እና የኢንዱስትሪ እድገትን ያፋጥናል ሲሉም አብራርተዋል፡፡
የኮቪድ ወረርሽኝን እንደ ማንቂያ ደወል የጠቀሱት ኪፓንያ፤ ራስን መቻል አስፈላጊ እንደሆን አፅንዖት ሰጥተዋል። ሀገራት ድንበሮቻቸውን ዘግተው በራሳቸው ገበያ ላይ መተማመን ከቻሉ፤ 1.4 ቢሊዮን ሕዝብ ያላት አፍሪካ ሰፊ አቅሟን መጠቀም መማር አለባት ሲሉ ተከራክረዋል።
"በአፍሪካ ለምን አምናለሁ? በአፍሪካ የማምነው ብቃት ያላቸው ሰዎች፣ ውብ መሬት እና በሌላው ዓለም ጥቅም ላይ የሚውሉ አብዛኛዎቹ ግብዓቶች ከአፍሪካ የሚመጡ መሆናቸውን ስለማውቅ ነው። እኛ ጋር ሁሉም ነገር አለ።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X