የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለቀጣይ አራት ዓመታት ከ7 በመቶ በላይ ዓመታዊ ዕድገት እንደሚያስመዘግብ ተነገረ
16:33 27.02.2026 (የተሻሻለ: 16:34 27.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ለቀጣይ አራት ዓመታት ከ7 በመቶ በላይ ዓመታዊ ዕድገት እንደሚያስመዘግብ ተነገረ
"ሪሰርች ኤንድ ማርኬትስ" የተሰኘው ተቋም ባወጣው አዲስ የዘርፉ የትንበያ ሪፖርት መሠረት፤ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዘርፍ ከ2026 እስከ 2029 በአማካይ የ7.8 በመቶ ዓመታዊ ዕድገት ያሳያል።
ሪፖርቱ ለዕድገቱ በምክንያትነት የጠቀሳቸው ቁልፍ ጉዳዮች፦
◻ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ አዳዲስ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣
◻ የመንግሥት የ10 ዓመት የልማት ዕቅድ፣
◻ የባንክ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት መደረጉ።
ዘርፉ ተስፋ ሰጪነቱ እንዳለ ሆኖ የብር መዳከምና ቀጣናዊ ውጥረቶች ተግዳሮት ሊሆኑ እንደሚችሉ መመላከቱን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ሪፖርቱን ጠቅሶ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X