ኮንጎ ሪፐብሊክ እና ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የ9 ሺህ ሜጋ ዋት የጋራ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኢነርጂ ፕሮጀክት ሊጀምሩ ነው
13:11 27.02.2026 (የተሻሻለ: 13:14 27.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኮንጎ ሪፐብሊክ እና ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የ9 ሺህ ሜጋ ዋት የጋራ የሃይድሮ ኤሌክትሪክ ኢነርጂ ፕሮጀክት ሊጀምሩ ነው
ሁለቱ ሀገራት ፕሮጀክቱን በኮንጎ ወንዝ ላይ ለመገንባት የሚያስችል የጋራ ፕሮግራም እያዘጋጁ እንደሚገኙ አንድ የአካባቢው የዜና ምንጭ ዘግቧል።
በዲአርሲ በፒዮካ-ቶምቤ ጣቢያ ላይ በሚያተኩረው የፕሮጀክቱ አካል የ6,120 ሜጋ ዋት አነስተኛ ማመንጫ ለመገንባት ታቅዷል።
በኮንጎ ሪፐብሊክ የሊንዞሎ፣ እምባንዛ-ንዱንጋ እና ኪንቴሌ ጣቢያዎች በአጠቃላይ እስከ 2,710 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንደሚኖራቸው የመጀመሪያ ደረጃ ጥናቶች ያሳያሉ።
ይህ ትብብር በሁለቱ ሀገራት ውስጥ የሚታየውን የኃይል እጥረት ለቅረፍ ያለመ እንደሆነ ተነግሯል፦
▪ በኮንጎ ብራዛቪል የማዕድን ዘርፉ ወደ 3,500 ሜጋ ዋት የሚጠጋ እጥረት ይገጥመዋል፣
▪ በኪንሻሳ እጥረቱ ወደ 1,000 ሜጋ ዋት አካባቢ ይገመታል።
“የኮንጎ ወንዝ እንደ የጋራ ሀብት እና ሚዛናዊ ቀጣናዊ የኢነርጂ ትስስር አንቀሳቃሽ ተደርጎ ይቆጠራል” ሲሉ የኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የውኃ ሀብት ሚኒስትር አይሜ ሞሌንዶ ሳኮምቢ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X