ኢትዮጵያዊቷ ሴት መካኒክ የተባበሩት መንግሥታት የክብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኑ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያዊቷ ሴት መካኒክ የተባበሩት መንግሥታት የክብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኑ
ኢትዮጵያዊቷ ሴት መካኒክ የተባበሩት መንግሥታት የክብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኑ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 27.02.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያዊቷ ሴት መካኒክ የተባበሩት መንግሥታት የክብር ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኑ

በደቡብ ሱዳን የተባበሩት መንግሥታት የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ውስጥ በመካኒክነት በማገልገል ላይ የሚገኙት ሻለቃ ትዕግስት ፈረደ፤ በተለምዶ የወንድ ሥራ ተብሎ በሚቆጠረው ሙያ ላበረከቱት ላቅ ያለ አስተዋጽኦ የክብር ሜዳሊያ ተሸልመዋል።

በምዕራብ ኢኳቶሪያ (ያምቢዮ) በተሠማራው የኢትዮጵያ ሰላም አሰከባሪ ኃይል አባል የሆኑት ሻለቃ ትዕግስት፤ የሰላም አስከባሪ ተሽከርካሪዎች ሁልጊዜ ለተልዕኮ ዝግጁ እንዲሆኑ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና በመጫወታቸው ነው እውቅናውን ያገኙት፡፡

"ሁሉም የምጠግናቸው ተሽከርካሪዎች ተስፋን ይሰንቃሉ። ደህንነታቸው ተጠብቆ ሲንቀሳቀሱ ለሰላም የበኩሌን እንደተወጣሁ ይሰማኛል። ይህንን ሜዳሊያ በማጥለቄ በሰላም ማስከበር ሥራ ውስጥ ትንሽ የሚባል ሚና እንደሌለ ተገንዝቤያለሁ" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ ያገለገሉ ሲሆን ከደቡብ ሱዳን በፊት የመጀመሪያ ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ተልዕኳቸውን በሱዳን ተወጥተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0