የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 170 ሺህ ዜጎችን ከጎርፍ መፈናቀል ማዳኑን አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 170 ሺህ ዜጎችን ከጎርፍ መፈናቀል ማዳኑን አስታወቀ
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 170 ሺህ ዜጎችን ከጎርፍ መፈናቀል ማዳኑን አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.02.2026
ሰብስክራይብ

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር 170 ሺህ ዜጎችን ከጎርፍ መፈናቀል ማዳኑን አስታወቀ

ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ በአዋሽ፣ በሪፍት ቫሊ እና በኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ላይ ባከናወናቸው የጎርፍ መከላከል ሥራዎች 170 ሺህ ነዋሪዎችን ከመፈናቀል፣ 30 ሺህ ሄክታር የእርሻ መሬትን ደግሞ ከውድመት መታደጉን አስታውቋል።

ይህ የተሰማው ሚኒስቴሩ በዘርፉ ከተሠማራ (ኤስ. ደብሊው.ኤስ) አማካሪ ድርጅት ጋር በመሆን በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ ያከናወነው የተግባራዊነት ጥናት ሪፖርት በሐዋሳ ከተማ ለባለድርሻ አካላት ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ፤ ጥናቱ ቀደም ሲል የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ መከላከል ሥራ በዘላቂ ጥናትና ፕሮጀክቶች ለመተካት እየተከናወነ ያለው ተግባር አካል መሆኑን ገልፀዋል።

በጥናቱ የተገኙ ውጤቶችን መሠረት በማድረግ በሌሎች የሀገሪቱ ተፋሰሶች ላይም ተመሳሳይ የጎርፍ መከላከል ስትራቴጂዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ታቅዷል መባሉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0