ኢትዮጵያ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ልትሰጥ ነው
14:03 26.02.2026 (የተሻሻለ: 14:04 26.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ትምህርትን ከአንደኛ ደረጃ ጀምሮ ልትሰጥ ነው
የትምህርት ሚኒስቴር የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ለማሳካት የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ክህሎት ትምህርትን ከአንደኛ እስከ 12ኛ ክፍል ባለው የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ለማካተት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ ጅምር ከዲጂታሉ ዓለም ጋር እኩል የሚራመዱ፣ ብቁና ተወዳዳሪ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ለማፍራት ብሎም ሀገሪቱን በዲጂታል ዘርፍ ተመራጭ ለማድረግ ትልቅ መሠረት እንደሚጥል ታምኖበታል ተብሏል።
በተያያዘም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ መምህራንና ተማሪዎች የዲጂታል ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ በአምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ሥልጠና ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘገባ አመላክቷል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X