አሜሪካ በኩባ የባሕር ዳርቻ በጀልባ የፈጸመችው ትንኮሳ ሁኔታዎችን ለማካካር ያለመ ነው - የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ለስፑትኒክ

አሜሪካ በኩባ የባሕር ዳርቻ በጀልባ የፈጸመችው ትንኮሳ ሁኔታዎችን ለማካካር ያለመ ነው - የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ለስፑትኒክ
የአሜሪካን ባንዲራ የሚያውለበልብ ጀልባ ወደ ኩባ የባሕር ክልል በመግባት ተኩስ መክፈቱን ተከትሎ የኩባ ድንበር ጠባቂዎች በወሰዱት አጸፋዊ እርምጃ በጀልባው ላይ የነበሩ አራት ሰዎች መገደላቸውን የኩባ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር ረቡዕ ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ስለ ሁኔታው እስካሁን የታወቁ መረጃዎች፦
▪ ፍሎሪዳ ውስጥ የተመዘገበው ሕገ-ወጥ የፍጥነት ጀልባ የካቲት 25 ቀን በኩባ የግዛት ውሃ ክልል ውስጥ በመግባት ከቪላ ክላራ ግዛት በአንድ የባሕር ማይል ባነሰ ርቀት ላይ ተቃርቦ እንደነበር ታውቋል።
▪ ሕግ መተላለፉን ተከትሎ የድንበር ጥበቃ ቡድን ሲቀርብ ከጀልባው በተከፈተ ተኩስ የጥበቃ መርከቡ አዛዥ ቆስለዋል።
▪ ከጥቃት ፈጻሚዎቹ ቢያንስ አራቱ ሲገደሉ ስድስቱ ደግሞ ቆስለዋል። የቆሰሉት የሕክምና እርዳታ እንዲያገኙ ተደርጓል።
▪ በጀልባው ላይ ተይዘው በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች በሙሉ በአሜሪካ የሚኖሩ ኩባውያን ሲሆኑ ከሟቾቹ አንዱ ኩባዊ ነው።
▪ ተጠርጣሪዎቹ የሽብርተኝነት ዓላማ እንደነበራቸው አምነዋል ሲል የኩባ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር አስታውቋል።
▪ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋሽንግተን በድርጊቱ ውስጥ ተሳትፎ የላትም ብሏል።
▪ እንደ አንድ የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገባ ከሆነ ጀልባው የአሜሪካ ባሕር ኃይልም ሆነ የባሕር ዳርቻ ጥበቃ ንብረት ሳይሆን ለንግድ አገልግሎት የተመዘገበ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X